.png)
ከሮቤል ሔኖክ
ድሬደዋ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በአስተዳደር የምትመራ ሁለተኛዋ ከተማ ናት:: ድሬደዋ ከኦሮሚኛ ወደ አማርና ሲተረጎም "የመድሀኒት ሜዳ" ማለት ሲሆን ከሶማሊኛ ወደ እንግሊዘኛ ሲረጎም ደግሞ "the place that Dir conquered or hit with his spear" የሚል ትርጓሜ እንዳለው በሱማሊኛ የተጻፉ ጽሁፎች ይጠቁማሉ::
የድሬደዋ አስተዳደር በሁለት ወረዳዎች የተከ ፈለ ሲሆን አንደኛው ኢሳ ሁለተኛው ጉርጉራ ይሰኛሉ:: በኢትዮጵያ ፓርላማ 2 መቀመጫ ቦታም አላቸው:: በድሬደዋ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ሲገኝ በከተማዋ ደግሞ 'አባ ጤና ደጃዝማች ይልማ ኢንተርናሽ ናል ኤርፖርት""; አንድ ስታዲየም; የምድር ባቡር እና የተለያዩ የገበያ ቦታዎች ይገኛሉ::
የአዲስ አባባ ጅቡቲ ምድር ባቡር መስመርን ተከትሎ በ1902 አ.ም የተቆረቆረችው ድሬደዋ ከአስር አመታት ወዲህ ለሁለት ጊዜያት በጎርፍ አደጋ መመታቷ የሚዘነጋ አይደለም:: በነዚህ የጎርፍ አደጋዎች በርከት ያለ ሰው ሕይወት እና የንብረት ላይ አደጋ ከመድረሱ በተጨማሪ ለብዙዎች መሰደድ ምክንያት ሆኗል::
በወቅቱ የዓለማችንን ሚዲያ ትኩረት ሥቦ የነበረው የድሬደዋ በጎርፍ አደጋ መጥለቅለቅን ተከትሎ ዛሬ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ባራክ ኦባማ በሥፍራው ተገኝተው መመልከታቸውን የምናስታውስ አለን? በፎቶ ግራፉ ላይ የምንመለከተው ኦባማ ኦገስት 30 2006 በድሬ ደዋ ከተማ በጎርፍ አደጋ የደረሰባቸውን አካባቢዎች ሲጎበኙና አደጋ የደረሰባቸውን ወግኖቻችንንም ሲያጽናኑ ነው:: በፎቶ ግራፉ ላይ አብረዋቸው የምናያቸው ኢትዮጵያውይው አቶ አበራ ቶላ ሲሆኑ እኚህ ሰው የኦክስፋም አሜሪካ የቀጠና ዳይሬክተር ናቸው:: አቶ አበራ ቶላ ለኦባማ ስለደረሰው አደጋ ገለጻ አድርገው ኦባማን አስጎብኝተዋል:: ኦባማም ኦክስፋም አሜሪካ በድሬደዋ በወቅቱ በደረሰው አደጋ ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አድርሰዋል:: ዛሬስ?
150 ሰው ያለቀበት: ከ12ሺህ ሰዎች በላይ ጉዳት ባደረሰው አደጋ ወቅት ኦባማ እንደደረሱት በኢትዮጵያ መልካም አስተዳድር ሰፍኖ አንጨላጭሎ የነበረው የዴሞክራሲ በር እንዳይዘጋ ምን ያግዙን ይሆን? በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ ብዙዎች የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ከምርጫው በፊት ኢሕአዴግ ለዴሞክራሲ የከፈተው በር አሁን ጥርቅም ተደርጎ ተዘግቷል:: ኦባማ ልክ በድሬደዋው አደጋ እንደደረሱት ሁሉ ዛሬም በኢትዮጵያ ለሰብአዊ መብቶች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ብለን እንጠብቅ??
በነገራችን ላይ ድሬደዋ ከአዲስ አበባ 310 ማይልስ ርቀት ላይ የምትገኝ ከታላላቅ የኢትዮጵያ የንግድ ከተሞች መካከል አንዷ ናት:: በድሬደዋ አስተዳደር ካውንስል ውስጥ ካሉት ሕዝቦች መካከል 40% ኦሮሞዎች: 27.7% አማሮች: 13.9% ሶማሊዎች: 4.5% ጉራጌዎች (2.3% ሰባት ቤት: 0.8% ሶዶ: 1.4% ስልጤ) እና 5.9% የሌሎች ብሄሮች ተወላጅ ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ:: የድሬደዋ ዋና ብሔራዊ ቋንቋ አማርኛ ሲሆን 63.2% የእስልምና; 34.5% የኦርቶዶክስ ክርስቲያን; 1.5% የፕሮቴስታንት; 0.7% የካቶሊክ እና 0.1% የሌሎች እምነት ተከታዮች ይኖራሉ::ð
No comments:
Post a Comment