Thursday, December 4, 2008

ቴዲን የፖለቲካ እስረኛ የሚያስመስሉት 8 ነጥቦች



1 የቴዲ አፍሮ ጉዳይ ፖለቲካዊ መምሰሉና ጠበቃው አቶ ሚሊዮን አሰፋ የኢህአዴግ ደጋፊና የምርጫ ቦርድ ጠበቃ ሆኖ፣ የቅንጅት አመራሮች እስር ቤት በነበሩበት ወቅት እስሩን ደግፎ ሞት ሊፈረድባቸው ይገባል እያለ በመንግሥት ራዲዮና በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በየቀኑ መግለጫ ሲሰጥ የነበረ ጠበቃ መሆኑ፤
2 ሁለተኛ ወንጀል ችሎት የነበሩትና ለሁለት ዓመታት የዘለቀውንና የቅንጅት አመራሮች ... የተከሰሱበትን ችሎት በቀኝ ዳኝነት ሲያስችሉ የነበሩት አቶ ልዑል ወ/ማርያም በድንገት 8ኛ ወንጀል ችሎት መገኘት፤ (አቶ ልኡል ለበርካታ ጋዜጠኞች መሰደድ: መታሰር እና መታረዝ ዋና ምክንያት ነው::) ሰሞኑን አዲስ አበባ ከተማ በተደረገው የታላቁ ሩጫ ውድድር ላይ የቴዲን ስም የጠሩና ፎቶ ግራፉ ያለበትን ቲሸርቱን የለበሱ መታሰራቸው፤ በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል የሚመራው መኢአድ በአዲስ አበባ አደባባዮች የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርግ በቴዲ አፍሮ ሙዚቃዎች እንዳይቀሰቅሱ መከልከላቸው፤
3 ምኒልክ ሆስፒታል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ኦርጅናል የአስከሬን የምርመራ ውጤትን 'ተሳስቷል' በሚል መቀየሩ፤
4 ችሎት በሚኖርበት ጊዜ በርካታ ቁጥር ያላቸው ደህንነቶች ችሎቱን ማጨናነቃቸውና ችሎት ተከታታዩን ሰው ማስጨነቃቸው፤
5 በቴዲ የፍርድ ቤት ንግግር ያለቀሱ አድናቂዎቹ መታሰርና መንገላታት:
6 የቅንጅት አመራሮችን ሲጠብቁ የነበሩ የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊሶች ሳይታክቱ በችሎት በመገኘት ጥብቅ ቁጥጥር ማድረጋቸው፤
7 ቃሊቲ ከገባ በኋላ ለብቻው መታሰሩ፤
8 ከተወሰኑ ሰዎች በስተቀር ማንም እንዳይጠይቀው መከልከሉ፤ በመኪና ሰው ገጭተሃል በሚል ተጠርጥሮ ለታሰረ ሰው ያልተለመዱ ድርጊቶች ናቸው።

No comments: