በትንሾቹ የአሳ ማስገሪያ ጀልባዎች የኤደንን ባሕረ ሰላጤ ተሻግረው ወደ የመን ለመግባት ሲሞከሩ ሰጥመው ህይወታቸውን ያጡ ስድሳ የጀልባ ስደተኞች አስከሬኖች በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በየመን ጠረፍ አቅራቢያ መገኘቱን ድንበር የማይገድበው የሀኪሞች ድርጅት MSF አስታወቀ።
ከሱማሊያ ወደ የመን ለመግባት ሲሞክሩ በባህር ሰጥመው ሲሞቱ እነዚህ የመጀመሪያዎቹ አለመሆናቸውን የጠቆመው MSF በዚህ ዓመት ብቻ ከ400 በላይ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ስደተኞች በዚህ ባህር ውስጥ ሰጥመው ቀርተዋል:: አሁን ከሞቱት ወደ ስድሳ የሚጠጉት ስደተኞች መካከል ምን ያህሉ የሶማሌያ: ምን ያህሉ የኢትዮጵያ ስደተኞች መሆናቸው አልታወቀም:: በየመን የሚገኙት የድርጅቱ ባለስልጣን አንድሪያስ ኩፒፓስ ለጀርመን የዜና ወኪል እንዳስረዱት፡ ስደተኞቹ የሞቱት ህገ ወጦቹ የጀልባዎቹ ሰራተኞች በተለያየ ምክንያት ባሕር ውስጥ እንዲዘሉ ባስስገደዱበት ጊዜ ነበር።
በሕገወጥ መንግድ ባህርን አቋርጦ የአንድን ሀገር ድንበር ሰብሮ ለመግባት በሚደረግ ትግል ምናልባት ድንበር ጠባቂ ፖሊስ እጅ ላለመግባት ሲሉ የጀልባዎቹ ሰራተኞች (ደላሎች) ስደተኞችን ወደ ባህር እንዲሰምጡ እንደሚያስገድዷቸው ያወሱት እኚሁ ባለስልጣን በተለይ በዚህ አመት በኤደን ባህር የሞቱት ቁጥር ከፍ ማለቱ አሳስቧቸዋል:: በሀገር ውስጥ ያለውን ፖለቲካዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ችግር ለመቋቋም የተሳናቸው ኢትዮጵያው ያን: ኤርትራዊያን: ሶማሊያውያን ስደተኞች በሊቢያ ወደ ጣሊያን: በሞሮኮ ወደ ስፔን: በቱርክ ወደ ግሪክ ለመግባት በሚያደርጉት የባህር ጉዞ በርካቶች ለሞት ይዳረጋሉ::
እነዚህ ሁሉ መከራዎች አልፈው ለስኬት የበቁ ጥቂት ሰዎች እንደሚናገሩት ""የአንድን ሀገር ድንበር ስታቋርጥ መሞት: መታሰር ወይም የምትፈልገው ሀገር መድረስ ይኖራል:: እነዚህን ሁሉ ለማድረግ ገንዝብ ያስፈልጋል:: የምታቋርጠበት ሀገር ፖሊስ ገንዝብ ከፍለህ እዛ እንደደረስክ ስለሚያውቅ ሊረዳህ አይችልም:: እንደውም ገንዝብ ካልከፈልክ እስር ቤት ትማቅቃለህ"" ይላሉ::
በየመን የኤደን ባህረ ሰላጤን አቋርጠው ምናልባት ከሞት እና በፖሊስ ካለመያዝ ቢተርፉ እንኳ የመን ውስጥ ገብቶ ሥራ ሰርቶ ለመኖር እጅግ አስቸጋሪ እንደሆነ በርከት ያሉ በስፍራው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ይናገራሉ:: በዩናይትድ ኔሽን ተመዝግቦ እንኳ ወደ 3ኛ ሀገር ለመሄድ በየመን እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ እንዳለ የሚናገሩት ስደተኞች ''የየመን ፖሊሶች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰጠውን የስደተኛነት ወረቀት እስከመቅደድ ይደርሳሉ:: ለዚህም የሚናገራቸው የለም"" ይላሉ:: አንድ በሱማሊያ አድርጎ የመን የገባ ስድተኛ ሲናገር ''ሞትን አምልጬ የመን ገባሁ: አሁንም ላለመሞት እየታገልኩ ነው"" ይላል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ ሕትመት እየገባን ባለንበት ወቅት የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ባሰራጨው ዘገባ በዚሁ በየመን የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ላለመያዝ ፣ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ሰዎችን በአደን ባህረ-ሰላጤ በኩል ወደ የመን የሚያሸጋግሩ ሰዎች 240 ስደተኞች ከመርከብ ወደ ባህር አየዘለሉ እንዲዋኙ በማስገደዳ ቸው 18 ሲሰጥሙ ከ 70 በላይ የሚሆኑት ደብዛቸው መጥፋቱ ተነገረ። የተረፉት ደቡብ የመን ከተማ ፣ አህዋር መግባታቸው ተገልጿል። ስደተኞቹ፣ በአመዛኙ ከሶማልያ ጥቂቶቹም ኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ተመልክቷል። ð
Thursday, December 4, 2008
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment