
ወደ ታሪኩ ከመግባታችን በፊት ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ፤ ዛሬ አብሮሽ በትዳር ያለ ጓደኛሽ ወይም በወሲብ የምታውቂው እጮኛሽ የኤች አይቪ ቫይረስ በደሙ እንዳለ እያወቀ ካንቺ ጋር አልጋ ላይ ቢወድቅና አንቺም ትዳር ላይ ከገባችሁ በኋላ ይሕንን ብታውቂ ምን ታደርጊያለሽ? ያንቺን ውሳኔ እወቂና ምህረት አስቻለው ያጠናቀረውን እውነተኛ ታሪክ ተከታተይ።
ባህር ዳር ከተማ ውስጥ በግ ተራ ተብሎ የሚጠራ አካባቢ ነው፡፡ ምሽት አሥራ ሁለት ሠዓት ገደማ ወደ አንድ ደሳሳ ቤት ጠጋ ብለን በር አንኳኳን ምንም ምላሽ አላገኘንም፡፡ ደግመን ስናንኳኳ ግቡ የሚል የወንድ ድምፅ ከወደ ውስጥ ሠማን፡፡ የቆርቆሮውን በር ገፋ አድርገን ስንገባ ፊት ለፊት በግምት እድሜው ሦስት ዓመት የሚሆን ህፃን ፊት ለፊት ወንበር ላይ፣ አይናቸው ላይ መሀረብ ጣል አድርገው ጠባብ አልጋ ላይ ተንጋለው የተገኙ አዛውንት ተመለከትን፡፡ አዛውንቱ ህፃኑን እናቱን እንዲጠራ አዘዙት፡፡
ስሟ እንዲጠቀስ ያልፈለገችው ወ/ሮ ተወልዳ ያደገችው አዲስ ዘመን የሚባል አካባቢ እንደሆነ፤ ትዳር የመሠረተችውም (አዛውንቱን ያገባችው) በቤተሰብ በኩል እንደሆነ ገልፃልናለች፡፡ ጋብቻ የመሠረቱት 1986 ዓ.ም. ላይ ነበር፤ በዚያ ወቅት ባለቤቷ በጦር ሠራዊት ውስጥ ያገለግሉ እንደነበርም አስታውሳለች፡፡
ሦስት ልጆችን አፍርተዋል፡፡ የመጀመሪያው የአሥራ አራት፣ ሁለተኛዋ የዘጠኝ ዓመት፣ በር ከፍተን ስንገባ የተመለከትነው ህፃን ደግሞ የመጨረሻ ልጃቸው ሲሆን ሦስት ዓመቱ ነው፡፡ ከጡረታ በሚገኝ ገንዘብና አትክልት እየቸረቸረች ወይዘሮዋ ቤተሰባቸውን ታስተዳድራለች ልጆቿንም ታስተምራለች፡፡
“ባለቤቴ በተደጋጋሚ ይታመም ነበር፡፡ ሁለተኛዋ ልጄም ዘወትር ትታመም ስለነበር ጥርጣሬ አደረብኝ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ባለቤቴ ከጦር ሠራዊት ተሰናበተ፡፡ የባለቤቴም የዘጠኝ ዓመት ልጄም ህመም ቀን ከቀን እየበረታ መጣ፡፡ ባለቤቴ ይጠጣል በዚህም ዘወትር እንጋጫለን፡፡ ትዳራችን በብዙ መልኩ ችግር ውስጥ ገባ” ብላለች፡፡
ህፃን ልጇ በጣም መታመም ስለጀመረች ወደ ሆስፒታል መሄድ የግድ ሆነ፡፡ ለህፃኗ ምርመራ ከተደረገላት በኋላ የህፃኗ እናት መሆኗን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንድታመጣና እሷም የኤች.አይ.ቪ ምርመራ እንድታደርግ እንደተነገራት አስታውሳለች፡፡ የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በህፃኗም በእሷም ደም ውስጥ መኖሩ ተነገራት፡፡ ይህን ካወቀች በኋላ ትዳራቸው መፍረስ እንዳለበት በማመን ባለቤቷን እንዲፋቱ ጠይቃቸዋለች፡፡ ባለቤቷ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ፍርድ ቤት በማመልከት ፍቺ ጠይቃለች፡፡
ጉዳያቸው በመታየት ላይ እያለ ባለቤቷና ሌሎቹ ልጆቿ የኤች.አይ.ቪ ምርመራ አድርገው እነሱም ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ መኖሩ ሊታወቅ ችሏል፡፡ ይህ ደግሞ የወይዘሮዋን ቁጣ አባባሰው፡፡ “የልጃገረድ ባለቤቴ ነው፡፡ ከተጋባንም ወዲያ እኔ የማውቀው ነገር አልነበረኝም፡፡ እሱ ግን ስለህመሙ እያወቀ እንድንጋባ፤ ከዚያም እነዚህን ልጆች እንድንወልድ ማድረጉ በጣም አስቆጣኝ፡፡ በትዳር በቆየንባቸው ጊዜያት ሁሉ አንድም ቀን ምንም ብሎ አያውቅም” ትላለች፡፡
ወይዘሮዋ እንደምትለው፣ ቀደም ሲል በተለይም ገጠር እያለች ስለ ኤች.አይ.ቪ ብዙም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ባለቤቷና ህፃን ልጅዋ በተደጋጋሚ ይታመሙ ስለነበር ይህም ጥርጣሬ ይፈጥርባት የነበረ ቢሆንም የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በእሷና በባለቤቷ እንዲሁም በሦስት ልጆቿ ደም ውስጥ መገኘቱን መቀበል በጣም ፈታኝ ሆኖባት ነበር፡፡
ባለቤቷ፣ እሷና ሁለተኛ ልጇ ቫይረሱ በደማቸው መኖሩ እንደታወቀ ወዲያው ፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ጀምረዋል፡፡ “እያወቀ እኔን እንዳገባኝና እነዚህ ልጆችም እንዲፈጠሩ አደረገ ብዬ ባለቤቴን
ሠላም አሳጣሁት፡፡ ቤት ውስጥ ሠላም ጠፋ፡፡ ባለቤቴም ከቤት ወጥቶ ሔዶ ነበር፡፡ እኔም በአንድ በኩል ህመምና ድህነት፤ በሌላ በኩል ብስጭት አእምሮዬን እንድስት አደረገኝ፡፡ ጉዳያችንን ፍርድ ቤት እየተመለከተው እያለ እኔም እየተረጋጋሁ መጣሁ፡፡ ከባለቤቴ ጋር ተለያይቼ የማገኘው የተሻለ ነገር የለም፡፡ ምን አልባትም ህይወት ሊከብደኝ ይችላል ብዬ አሰብኩኝ” በማለት ትዳሯን የማፍረስ ሃሳቧን ቀይራ በይቅርታ ከባለቤቷ ጋር ለመኖር መወሰኗን ነገረችን፡፡
ህመም በርትቶባት በተለያዩ ጊዜአት ተኝታ ነበር፡፡ ባለቤቷም በተደጋጋሚ ይታመማሉ፡፡ ከሁሉም በይበልጥ የምትታመመው ግን ህፃን ልጇ ነች፡፡ ጐረቤቶች በተለያየ አጋጣሚ ሽንት ቤት እንዳትጠቀም በማድረግና በለሎች ነገሮች አግልለዋት ነበር፡፡ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ ግን ጐረቤቶቿ ከማግለል ይልቅ ሊያቀርቧት እንደሚፈልጉ፤ እሷ ግን ያለፈውን ትታ በይቅርታ እንደቀድሞ ከጐረቤቶቿ ጋር መቀራረብ አለመቻሏን በሀዘኔታ ገልፃልናለች፡፡
“ተመርምረን ራሳችንን ካወቅን ሁለት ዓመት ሆነን፡፡ በጣም አስቸጋሪ የሆነብኝ የሴቷ ልጄ ሁኔታ ነው፡፡ ዘጠኝ ዓመቷ ነው ግን ዘወትር ስለምትታመም ሠውነቷ ድቅቅ ያለ ነው” በማለት የሦስት ዓመቱን የመጨረሻ ልጇን ጭንቅላት በመዳሰስ “እሱን ነው የምታክለው” አለችን፡፡ “በቂ ምግብ ስለማታገኝም እንደሆነ አላውቅም መድሀኒቱን አልቻለችውም፡፡ ሁለት ጊዜ አስቀይሬላታለሁ፡፡ መድኃኒት የምትወስድበትን ሠዓት ለይታ ስለምታውቅ በዚያ ሠዓት ወደ መንደር ሔዳ ትጠፋብኛለች፡፡ የዋጠች መስላ ትተፋዋለች፡፡ እሷን ለመቆጣጠር ብዬ እኔም እሷም መድኃኒት የምንወስድበት ሠዓት አንድ ዓይነት አደረግኩት”
የመጀመሪያ ልጇ አሥራ አራት ዓመቱ ቢሆንም ስለ እናትና አባቱም ሆነ ስለታናሽ እህቱ ህመም የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ስለራሱ ውጤትም አልተነገረውም፡፡ ፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት የምትወስደው ህፃን ግን ሁሌም መድኃኒት ውሰጂ ስትባል ለምን እያለች ትጠይቃለች፣ ላለመውሰድም ትታገላለች፡፡ð
ባህር ዳር ከተማ ውስጥ በግ ተራ ተብሎ የሚጠራ አካባቢ ነው፡፡ ምሽት አሥራ ሁለት ሠዓት ገደማ ወደ አንድ ደሳሳ ቤት ጠጋ ብለን በር አንኳኳን ምንም ምላሽ አላገኘንም፡፡ ደግመን ስናንኳኳ ግቡ የሚል የወንድ ድምፅ ከወደ ውስጥ ሠማን፡፡ የቆርቆሮውን በር ገፋ አድርገን ስንገባ ፊት ለፊት በግምት እድሜው ሦስት ዓመት የሚሆን ህፃን ፊት ለፊት ወንበር ላይ፣ አይናቸው ላይ መሀረብ ጣል አድርገው ጠባብ አልጋ ላይ ተንጋለው የተገኙ አዛውንት ተመለከትን፡፡ አዛውንቱ ህፃኑን እናቱን እንዲጠራ አዘዙት፡፡
ስሟ እንዲጠቀስ ያልፈለገችው ወ/ሮ ተወልዳ ያደገችው አዲስ ዘመን የሚባል አካባቢ እንደሆነ፤ ትዳር የመሠረተችውም (አዛውንቱን ያገባችው) በቤተሰብ በኩል እንደሆነ ገልፃልናለች፡፡ ጋብቻ የመሠረቱት 1986 ዓ.ም. ላይ ነበር፤ በዚያ ወቅት ባለቤቷ በጦር ሠራዊት ውስጥ ያገለግሉ እንደነበርም አስታውሳለች፡፡
ሦስት ልጆችን አፍርተዋል፡፡ የመጀመሪያው የአሥራ አራት፣ ሁለተኛዋ የዘጠኝ ዓመት፣ በር ከፍተን ስንገባ የተመለከትነው ህፃን ደግሞ የመጨረሻ ልጃቸው ሲሆን ሦስት ዓመቱ ነው፡፡ ከጡረታ በሚገኝ ገንዘብና አትክልት እየቸረቸረች ወይዘሮዋ ቤተሰባቸውን ታስተዳድራለች ልጆቿንም ታስተምራለች፡፡
“ባለቤቴ በተደጋጋሚ ይታመም ነበር፡፡ ሁለተኛዋ ልጄም ዘወትር ትታመም ስለነበር ጥርጣሬ አደረብኝ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደግሞ ባለቤቴ ከጦር ሠራዊት ተሰናበተ፡፡ የባለቤቴም የዘጠኝ ዓመት ልጄም ህመም ቀን ከቀን እየበረታ መጣ፡፡ ባለቤቴ ይጠጣል በዚህም ዘወትር እንጋጫለን፡፡ ትዳራችን በብዙ መልኩ ችግር ውስጥ ገባ” ብላለች፡፡
ህፃን ልጇ በጣም መታመም ስለጀመረች ወደ ሆስፒታል መሄድ የግድ ሆነ፡፡ ለህፃኗ ምርመራ ከተደረገላት በኋላ የህፃኗ እናት መሆኗን የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንድታመጣና እሷም የኤች.አይ.ቪ ምርመራ እንድታደርግ እንደተነገራት አስታውሳለች፡፡ የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በህፃኗም በእሷም ደም ውስጥ መኖሩ ተነገራት፡፡ ይህን ካወቀች በኋላ ትዳራቸው መፍረስ እንዳለበት በማመን ባለቤቷን እንዲፋቱ ጠይቃቸዋለች፡፡ ባለቤቷ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ፍርድ ቤት በማመልከት ፍቺ ጠይቃለች፡፡
ጉዳያቸው በመታየት ላይ እያለ ባለቤቷና ሌሎቹ ልጆቿ የኤች.አይ.ቪ ምርመራ አድርገው እነሱም ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ መኖሩ ሊታወቅ ችሏል፡፡ ይህ ደግሞ የወይዘሮዋን ቁጣ አባባሰው፡፡ “የልጃገረድ ባለቤቴ ነው፡፡ ከተጋባንም ወዲያ እኔ የማውቀው ነገር አልነበረኝም፡፡ እሱ ግን ስለህመሙ እያወቀ እንድንጋባ፤ ከዚያም እነዚህን ልጆች እንድንወልድ ማድረጉ በጣም አስቆጣኝ፡፡ በትዳር በቆየንባቸው ጊዜያት ሁሉ አንድም ቀን ምንም ብሎ አያውቅም” ትላለች፡፡
ወይዘሮዋ እንደምትለው፣ ቀደም ሲል በተለይም ገጠር እያለች ስለ ኤች.አይ.ቪ ብዙም የምታውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ባለቤቷና ህፃን ልጅዋ በተደጋጋሚ ይታመሙ ስለነበር ይህም ጥርጣሬ ይፈጥርባት የነበረ ቢሆንም የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በእሷና በባለቤቷ እንዲሁም በሦስት ልጆቿ ደም ውስጥ መገኘቱን መቀበል በጣም ፈታኝ ሆኖባት ነበር፡፡
ባለቤቷ፣ እሷና ሁለተኛ ልጇ ቫይረሱ በደማቸው መኖሩ እንደታወቀ ወዲያው ፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ጀምረዋል፡፡ “እያወቀ እኔን እንዳገባኝና እነዚህ ልጆችም እንዲፈጠሩ አደረገ ብዬ ባለቤቴን
ሠላም አሳጣሁት፡፡ ቤት ውስጥ ሠላም ጠፋ፡፡ ባለቤቴም ከቤት ወጥቶ ሔዶ ነበር፡፡ እኔም በአንድ በኩል ህመምና ድህነት፤ በሌላ በኩል ብስጭት አእምሮዬን እንድስት አደረገኝ፡፡ ጉዳያችንን ፍርድ ቤት እየተመለከተው እያለ እኔም እየተረጋጋሁ መጣሁ፡፡ ከባለቤቴ ጋር ተለያይቼ የማገኘው የተሻለ ነገር የለም፡፡ ምን አልባትም ህይወት ሊከብደኝ ይችላል ብዬ አሰብኩኝ” በማለት ትዳሯን የማፍረስ ሃሳቧን ቀይራ በይቅርታ ከባለቤቷ ጋር ለመኖር መወሰኗን ነገረችን፡፡
ህመም በርትቶባት በተለያዩ ጊዜአት ተኝታ ነበር፡፡ ባለቤቷም በተደጋጋሚ ይታመማሉ፡፡ ከሁሉም በይበልጥ የምትታመመው ግን ህፃን ልጇ ነች፡፡ ጐረቤቶች በተለያየ አጋጣሚ ሽንት ቤት እንዳትጠቀም በማድረግና በለሎች ነገሮች አግልለዋት ነበር፡፡ ከተወሰነ ጊዜ ወዲህ ግን ጐረቤቶቿ ከማግለል ይልቅ ሊያቀርቧት እንደሚፈልጉ፤ እሷ ግን ያለፈውን ትታ በይቅርታ እንደቀድሞ ከጐረቤቶቿ ጋር መቀራረብ አለመቻሏን በሀዘኔታ ገልፃልናለች፡፡
“ተመርምረን ራሳችንን ካወቅን ሁለት ዓመት ሆነን፡፡ በጣም አስቸጋሪ የሆነብኝ የሴቷ ልጄ ሁኔታ ነው፡፡ ዘጠኝ ዓመቷ ነው ግን ዘወትር ስለምትታመም ሠውነቷ ድቅቅ ያለ ነው” በማለት የሦስት ዓመቱን የመጨረሻ ልጇን ጭንቅላት በመዳሰስ “እሱን ነው የምታክለው” አለችን፡፡ “በቂ ምግብ ስለማታገኝም እንደሆነ አላውቅም መድሀኒቱን አልቻለችውም፡፡ ሁለት ጊዜ አስቀይሬላታለሁ፡፡ መድኃኒት የምትወስድበትን ሠዓት ለይታ ስለምታውቅ በዚያ ሠዓት ወደ መንደር ሔዳ ትጠፋብኛለች፡፡ የዋጠች መስላ ትተፋዋለች፡፡ እሷን ለመቆጣጠር ብዬ እኔም እሷም መድኃኒት የምንወስድበት ሠዓት አንድ ዓይነት አደረግኩት”
የመጀመሪያ ልጇ አሥራ አራት ዓመቱ ቢሆንም ስለ እናትና አባቱም ሆነ ስለታናሽ እህቱ ህመም የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ ስለራሱ ውጤትም አልተነገረውም፡፡ ፀረ-ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት የምትወስደው ህፃን ግን ሁሌም መድኃኒት ውሰጂ ስትባል ለምን እያለች ትጠይቃለች፣ ላለመውሰድም ትታገላለች፡፡ð
No comments:
Post a Comment